የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን ለሦስት አዲስ የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጭዎች ፈቃድ ሰጠ

የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን ከሰፊ የፈቃድ ማመልከቻ ግምገማ ሂደት በኋላ ለሦስት (3) አዳዲስ የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጭዎች ፍቃድ በመስጠቱ የተሰማውን ደስታ ይገልጻል። በተጨማሪም ባለስልጣኑ የሦስቱን አዳዲስ አገልግሎት ሰጭዎች አስር (10) ተሿሚ እንደራሴዎችን ፈቃድ ያጸደቀ ሲሆን፣ የ አስራ አምስት (15) ቦርድ አባላት ሹመትንም አጽድቋል። የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ጀነራል ሃና ተኸልቁ ፈቃዱን ሐምሌ 3 ቀን 2018 ዓ.ም. […]
የካፒታል ገበያ ኢንቬስተሮች ቀን አውደ ርዕይ በስኬት ተጠናቀቀ

የኢትዮጵያ የካፒታል ባለስልጣን ከሰኔ 12 እስከ13 2018 ዓ.ም ያካሄደውን የሁለት ቀናት የኢንቬስተሮች አውደ ርዕይ በስኬት አጠናቋል። በአውደ ርዕዩ ላይ በርካታ ቁጥር ያላቸው ጎብኚዎች የጎበኙ ሲሆን፥ ስለ ካፒታል ገበያው እድሎች እና የኢንቨስትመንት አማራጮች ሰፊ ግንዛቤ ማስጨበጫ የተሰጠበት መርሃ -ግብር ሆኖ አልፏል።ለአወደ ርዕዩ ውጤታማ መሆን እና ለስኬታማነቱ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ላበረከቱ ባለድርሻ አካላት፣ ለተሳታፊዎች እና ለጉብኝዎች በሙሉ የኢትዮጵያ […]
የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን ከሉክሰምበርግ ልዑካን ቡድን አባላት ጋር ውይይት አደረገ

የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን በኢትዮጵያ የሉክስምበርግ አምባሳደር ከሆኑት ክቡርት ዣን ክራውዘር፣ ሻርዠ ደፌር አሪያን ሞያ እንዲሁም የመጀመሪያ ጸሀፊ ከሆኑት ማክስም ላድሪየርን ጋር በሉክሰምበርግ እና በኢትዮጵያ መካከል በካፒታል ገበያ ያለውን ትብብር ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ውጤታማ ውይይት አድርጓል።ውይይቱ ቀደም ሲል የነበሩ ግንኙነቶችን መሰረት አድርጎ የቀጠለ ሲሆን በኢትዮጵያ የሉክሰምበርግ ኢምባሲ የኢትዮጵያን የካፒታል ገበያ ልማት ሥራዎች ለመደገፍ በሚችላቸው የቴክኒክ ድጋፍ […]
የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን ለዩናይትድ ካፒታል ፋይናንሻል ሰርቪስ ኃ.የተ.የግ.ማህበር የኢንቨስትመንት ባንክ ፈቃድ ሰጠ

የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን (ባለስልጣኑ) የናይጄሪያው ዩናይትድ ካፒታል ግሩፕ ተቀጥላ ኩባንያ (Subsidiary) ለሆነው ዩናይትድ ካፒታል ፋይናንሻል ሰርቪስስ ኃ.የተ.የግ.ማህበር የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪነት ፈቃድ ሰጥቷል። ይህም ተቋሙን በኢትዮጵያ ውስጥ ተቀጥላ ኩባንያ በማቋቋም እንዲንቀሳቀስ ፈቃድ የተሰጠው የመጀመሪያው የውጭ ኢንቨስትመንት ባንክ ያደርገዋል። የተሰጠው ፈቃድ ድርጅቱ በኢንቨስትመንት ባንክ ዘርፍ ስር እንዲሠራ የሚፈቅድ ሲሆን፤ ባለስልጣኑ ከዚህ በተጨማሪ የአምስት (5) የቦርድ […]
የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን ከኦሮሚያ ሶቨሬን ፈንድ ጋር ተወያየ

የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን ከኦሮሚያ ሶቨሬን ፈንድ ጋር ተወያየ የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን ከኦሮሚያ ሶቨሬን ፈንድ ከፍተኛ ኃላፊዎች ጋር ፈንዱ በካፒታል ገበያው ስለሚሳተፍበት ሁኔታ ውይይት አደረገ፡፡ የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሃና ተኸልቁ በውይይቱ እንደገለጹት ፈንዱ በተለያዩ ግዙፍ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ያለውን አቅም ወደ ካፒታል ገበያው በማምጣት ተቋማዊ ዕድገቱን ከመገንባት ባለፈ ለሀገራዊው ገበያ መጠናከር ወሳኝ ሚና […]
የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት በኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን የመስክ ምልከታ አካሄዱ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን የዕቅድ አፈጻጸም ምልከታ እና አጠቃላይ የተቋማዊ ዝግጁነት ሁኔታን ለመገምገም ያለመ የመስክ ምልከታ አካሂደዋል። ምልከታው ባለሥልጣኑ የቁጥጥርና የሕግ ማዕቀፎችን በማጠናከር፣ በሰው ኃይል አቅም ግንባታ እና በዲጂታል ሥርዓቶች ውጤታማ አጠቃቀም ረገድ እየተከናወኑ ባሉ ተግባራት ዙሪያ ገንቢ ውይይት የተደረገበት ነበር። በጉብኝቱ ወቅት የባለሥልጣኑ ዋና […]
የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን ለ ፕራይም ካፒታል አ.ማ. ፈቃድ ሰጠ።

የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን ለ ፕራይም ካፒታል አ.ማ. የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪነት ፈቃድ ሰጥቷል። በዚህም ድርጅቱ ከባንክ ቡድን ውጭ በሆነ የኢንቨስትመንት ባንክ ዘርፍ እንዲሠራ ፈቃድ ተሰጥቶቷል። በተጨማሪም ባለስልጣኑ ለ ፕራይም ካፒታል አ.ማ. አራት (4) ተሿሚ እንደራሴዎችም ፈቃድ የሰጠ ሲሆን የዘጠኝ (9) የቦርድ አባላት ሹመትንም አጽድቋል። የአገልግሎት ሰጪነት ፍቃዱም በዛሬው እለት ማክሰኞ ሚያዚያ 13፣ 2018 ዓ […]
የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን የ6 ወራት የእቅድ አፈጻጸሙን ገመገመ

የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት የእቅድ አፈጻጸምን በተመለከተ ከሰራተኞቹ ጋር የውይይት መድረክ አካሂዷል። በውይይት መድረኩ ላይ የተገኙት የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ሀና ተኸልቁ ባለፉት ስድስት ወራት ተቋሙ ተጨባጭ የሆኑ ውጤቶችን ማስመዝገቡን ገልጸዋል። ዋና ዳይሬክተሯ እንደጠቀሱት በተለይም የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪዎች ፍቃድ ቁጥር መጨመሩን ፣የተለያዩ አክሲዮን ማህበራት የሰነደ ሙዓለንዋዮች ምዝገባ […]
አክስዮኖቻችሁን ማስመዝገብ ሲገባችሁ ላላስመዘገባችሁ አክስዮን ማህበራት የተሰጠ ማስጠንቀቂያ እና ለህብረተሰቡ የተሰጠ ማሳሰቢያ

አክስዮኖቻችሁን ማስመዝገብ ሲገባችሁ ላላስመዘገባችሁ አክስዮን ማህበራት የተሰጠ ማስጠንቀቂያ እና ለህብረተሰቡ የተሰጠ ማሳሰቢያ እንደሚታወቀው የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን የካፒታል ገበያውን ለመቆጣጠር በካፒታል ገበያ አዋጅ ቁጥር 1248/2013 አንቀጽ 3 መሰረት የተቋቋመ ተቋም ሲሆን ባለስልጣኑ ከሚያከናውናቸው ተግባራት ውስጥ አንዱም የሰነደ ሙአለ ንዋዮች ምዝገባ ነው፡፡ በአዋጅ ቁጥር 1248/2013 አንቀጽ 75 መሰረት ማንኛውም ለህዝብ የሚሸጥ ሰነደ ሙአለ ንዋይ ለሽያጭ ወይም […]
አስደሳች ዜና ለኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ!

የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣንለአዋሽ ካፒታል አ.ማ. የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪነት ፈቃድ በኢንቨስትመንት ባንክ (በባንክ ቡድን ውስጥ) ዘርፍ ሰጥቷል ። ይህ በገበያው ልማት ውስጥ ሌላው ቁልፍ ምዕራፍ ሲሆን፣ በአገሪቱ ውስጥ ያሉት የተፈቀደላቸው የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪነት ፈቃድ ጠቅላላ ቁጥር ወደ አስራ ሦስት (13) እንዲሁም የኢንቨስትመንት ባንኮች ጠቅላላ ቁጥር ወደ አራት (4) ከፍ አድርጓል። የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር […]