ECMA Gold

ሚዲያ

የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን ከኦሮሚያ ሶቨሬን ፈንድ ጋር ተወያየ የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን ከኦሮሚያ ሶቨሬን ፈንድ ከፍተኛ ኃላፊዎች ጋር ፈንዱ በካፒታል ገበያው ስለሚሳተፍበት ሁኔታ ውይይት አደረገ፡፡ የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሃና ተኸልቁ በውይይቱ እንደገለጹት ፈንዱ በተለያዩ ግዙፍ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ያለውን አቅም ወደ ካፒታል ገበያው በማምጣት ተቋማዊ ዕድገቱን ከመገንባት ባለፈ ለሀገራዊው ገበያ መጠናከር ወሳኝ ሚና […]

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ  አባላት የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን የዕቅድ አፈጻጸም ምልከታ እና  አጠቃላይ የተቋማዊ ዝግጁነት ሁኔታን ለመገምገም ያለመ የመስክ ምልከታ አካሂደዋል። ምልከታው ባለሥልጣኑ የቁጥጥርና የሕግ ማዕቀፎችን በማጠናከር፣ በሰው ኃይል አቅም ግንባታ እና በዲጂታል ሥርዓቶች ውጤታማ አጠቃቀም ረገድ እየተከናወኑ ባሉ ተግባራት ዙሪያ  ገንቢ ውይይት የተደረገበት ነበር። በጉብኝቱ ወቅት የባለሥልጣኑ ዋና […]

የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን ለ ፕራይም ካፒታል አ.ማ. የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪነት ፈቃድ ሰጥቷል። በዚህም ድርጅቱ ከባንክ ቡድን ውጭ በሆነ የኢንቨስትመንት ባንክ ዘርፍ እንዲሠራ ፈቃድ ተሰጥቶቷል። በተጨማሪም ባለስልጣኑ ለ ፕራይም ካፒታል አ.ማ. አራት (4) ተሿሚ እንደራሴዎችም ፈቃድ የሰጠ ሲሆን የዘጠኝ (9) የቦርድ አባላት ሹመትንም አጽድቋል። የአገልግሎት ሰጪነት ፍቃዱም በዛሬው እለት ማክሰኞ ሚያዚያ 13፣ 2018 ዓ […]

  የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት የእቅድ አፈጻጸምን  በተመለከተ  ከሰራተኞቹ ጋር የውይይት መድረክ አካሂዷል።   በውይይት መድረኩ ላይ የተገኙት የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር  ሀና ተኸልቁ ባለፉት ስድስት ወራት ተቋሙ ተጨባጭ የሆኑ ውጤቶችን ማስመዝገቡን ገልጸዋል።  ዋና ዳይሬክተሯ  እንደጠቀሱት በተለይም የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪዎች ፍቃድ ቁጥር መጨመሩን ፣የተለያዩ አክሲዮን ማህበራት  የሰነደ ሙዓለንዋዮች ምዝገባ […]