ምርመራ እና ማስፈጸም

የኢ.ካ.ገ.ባ በአዋጅ ቁጥር 1248/2013 የተሰጡ የተለያዩ የማስፈጸም ስልጣኖችን ይዟል። ዳይሬክቶሬቱ በኢ.ካ.ገ.ባ ቁጥጥር ስር ባሉ ግለሰቦች ወይም  ህጋዊ ሰውነት ባላቸው አካላት ሊፈጸሙ የሚችሉ የካፒታል ገበያ ህጎች እና መመሪያዎች ጥሰቶችን የማጣራት ኃላፊነት ተሰጥቶታል።

አጠቃላይ እይታ

ይህ ኃላፊነት  ፈቃድ የተሰጣቸውን አገልግሎት ሰጪዎች እንቅስቃሴ መገምገም እና አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ለህግ  ተገዥ አልሆኑም ተብለው የተጠረጠሩትን የመመርመር፣ የምግባር ጉድለት፣ ገበያን አላግባብ መጠቀም ወይም ሌሎች ባለስልጣኑ በበላይነት ምልከታ የሚያደርግባቸው ህጎች  ሲጣሱ ምርመራ ማድረግን ያጠቃልላል። በምርመራ ወቅት ዳይሬክቶሬቱ እንደ ገበያን ያለ አግባብ መጠቀም፣ የገበያ ሽፍጥ የመሳሰሉ  የካፒታል ገበያ ወንጀሎችን ወይም ሌሎች ፈቃድ ያላቸው ወይም ፈቃድ የሌላቸው ግለሰቦችን የሚያካትቱ ህገወጥ ተግባራትን የያዙ ማስረጃዎችን ሊያገኝ ወይም ጥርጣሬዎች ሊኖሩት ይችላል። እንደዚህ አይነት ግኝቶችም ፍትህ ሚኒስቴር እና የፌዴራል ፖሊስን ጨምሮ አግባብነት ላላቸው የህግ አስፈፃሚ  አካላት ሪፖርት ይደረጋሉ።

የምርመራ እና ህግን የማስፈጸም ዳይሬክቶሬት ግኝቶቹን ለኢ.ካ.ገ.ባ ውሳኔ ሰጭ አካል ሪፖርት ያደርጋል እንዲሁም፤ ለመፍትሄ እርምጃዎች እና/ወይም ተገቢውን  የህግ ማስፈጸሚያ እርምጃለመውሰድ የሚረዱ ምክሮችን ያቀርባል። ከዚሀ በተጨማሪ የህግ ማስፈጸሚያ ውሳኔዎችን ውጤት የመተግበር እና የመከታተል ሃላፊነትም አለበት።