ECMA / ኢካገባ

የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን 18ኛውን የሰንደቅ አላማ ቀን አከበረ

photo 2025 10 13 11 48 42

ባለስልጣኑ በመላ ሀገሪቱ እየተከበረ የሚገኘውን 18ኛውን የሰንደቅ አላማ ቀን  ከሰራተኞች  ጋር በመሆን የብሄራዊ መዝሙር በመዘመር እና በዓሉን በሚመለከት የተዘጋጀ የመወያያ ሰነድ ላይ  ውይይት በማድረግ አክብሯል፡፡

በውይይቱ ለኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ ክብር በአባቶቻቸን የተከፈለው ዋጋ ትልቅ መሆኑ የተጠቀሰ ሲሆን ቀጣይነት ባለው መልኩ የአሁኑ ትውልድም  የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ ክብር ጠብቆ ማቆየት እንዲችል መስራት እንደሚገባም በውይይቱ ተነስቷል፡፡

የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን የሀገራችን የኩራት  መገለጫ የሆነው ሰንደቅ አላማችን የሚከበርበትን 18ኛውን የሰንደቅ አላማ ቀን በስኬት  በማክበሩ ደስታ ይሰማዋል፡፡

photo 2025 10 13 11 49 34