
አዲስ አበባ
ሀምሌ 17/2017 የኢካገባ
የኢትዮጵያ የካፒታል ገብያ ባለስልጣን እና የኢትዮጵያ የማስማማት እና የግልግል ዳኝነት ማዕከል በጋራ በሚሩባቸው የትብብር ማዕቀፍ ዙሪያ በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ውይይት አካሂደዋል፡፡
በውይይቱ የኢትዮጵያ የካፒታል ገብያ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሃና ተኸልኩን ጨምሮ የኢትዮጵያ የማስማማት እና የግልግል ዳኝነት ማዕከል ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ተሳትፈዋል፡፡

በጋራ ውይይቱ አማራጭ የግጭት መፍቻ ዘዴዎችን በተመለከተ እንዲሁም አማራጭ የግጭት መፍቻ ዘዴዎች በካፒታል ገበያ ውስጥ ስላላቸው ከፍተኛ ሚና ውይይት ተደርጓል ፡፡
የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን በካፒታል ገበያው ውስጥ የሚኖሩ ግጭቶች በሽምግልና፣ በግልግል ዳኝነት እንዲፈቱ ስለግልግል ዳኝነት አሰራር እና ከግልግል ዳኝነት ጋር የተያያዙ ወጪዎችን በተመለከተ በካፒታል ገበያ አዋጅ ቁጥር 1248/2013 የተሰጡትን ተግባራት ለመከወን የረዥም ግዜ ልምድ ካለው ከኢትዮጵያ የማስማማት እና የግልግል ዳኝነት ማዕከል ጋር በቅንጅት ለመስራት ያለውን ተነሳሽነትም ገልጿል፡፡