የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ የቁጥጥር ሳንድቦክስ በኢትዮጵያ ካፒታል ገበያዎች ባለስልጣን (ECMA) የተቋቋመ ማዕቀፍ ሲሆን የንግድ ድርጅቶች አዳዲስ የካፒታል ገበያ ምርቶችን እና አገልግሎቶችን ቁጥጥር በሚደረግበት አካባቢ ውስጥ እንዲሞክሩ ያስችላቸዋል። ይህም አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች ወደ ሰፊው ገበያ ከመድረሳቸው በፊት ደህንነታቸው የተጠበቀ እና ጠቃሚ መሆናቸውን ለማረጋገጥ ይረዳል።
ሳንድቦክሱ የሚከተሉትን ጨምሮ ለተለያዩ ድርጅቶች ክፍት ነው።
ተሳታፊዎች አነስ በሚሉ የቁጥጥር እንቅፋቶች/ማእቀፎች ምርቶቻቸውን ደህንነቱ በተጠበቀ አካባቢ መሞከር፣ ከተቆጣጠሪዎች የተበጀ ምክር እና መመሪያን መቀበል፣ ከባለድርሻ አካላት ተአማኒነትን ማግኘት እና ለገበያ ለመቅረብ የሚወስድባቸውን ጊዜ ማፋጠን ይችላሉ። ተሳትፎው ለሙከራ እና ለልማት አስፈላጊ የሆኑ ወሳኝ መሠረተ ልማቶችን እና የመረጃ ቋቶችን ያቀርባል። ይህ ፕሮግራም ለተሳታፊዎች የገንዘብ ድጋፍ እንደማይሰጥ ልብ ሊባል የሚገባው ጉዳይ ነው።
ፍላጎት ያላቸው ወገኖች በመጀመሪያ ከሳንድቦክሱ ቡድን ጋር በመወያየት ሃሳባቸውን መወያየት አለባቸው። ተስማሚ ሆኖ ከተገኘ በተዘጋጀው የኦንላይን መድረክ በኩል ዝርዝር ማመልከቻ ማስገባት ይችላሉ። ማመልከቻዎች የሚገመገሙት አስቀድሞ በተገለጸው የብቃት መስፈርት መሰረት ነው፣ እናም የተሳካላቸው አመልካቾች የሙከራ እቅድ ለማውጣት እና ለማስፈጸም ከተቆጣጠሪዎች ጋር ይተባበራሉ/አብረው ይሰራሉ።
የሚሰጠው ድጋፍ የሚከተሉትን ያካትታል:-
ሳንድቦክሱ ለሁሉም የፋይናንስ ፈጠራዎች ክፍት ቢሆንም፣ በተለይም የፋይናንስ አካታችነትን በእጅጉ የሚያሻሽሉ፣ የሸማቾች ጥበቃን የሚያሻሽሉ፣ ክፍያዎችን የሚያመቻቹ ወይም አጠቃላይ የፋይናንስ መሠረተ ልማቶችን በኢትዮጵያ የሚያጠናክሩ ቴክኖሎጂዎችን በደስታ ይቀበላል።
የሙከራው ደረጃ እስከ 12 ወራት ሊቆይ ይችላል፣ ነገር ግን የቆይታ ጊዜው እንደ ፕሮጀክቱ ልዩ ፍላጎቶች እና እንደ መጀመሪያዎቹ የሙከራ ወቅቶች ውጤቶች ሊለያይ ይችላል።
የሙከራ ወቅቱ ሲጠናቀቅ ተሳታፊዎች ስለ ግኝታቸው እና ውጤቶቻቸው ዝርዝር ሪፖርት ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል። በዚህ ሪፖርት ላይ በመመስረት የምርቱን ወይም የአገልግሎቱን የወደፊት ሁኔታ በሚመለከት (ወደ ሙሉ ገበያ ማሰማራት መሸጋገር፣ ተጨማሪ ሙከራ፣ ወይም ስራው መቆም አለበት በሚለው ዙሪያ) ውሳኔ ይወሰዳል።
This public notice is directed at publicly held companies established or raising capital through public subscription under the Commercial Code of Ethiopia. Specifically, it concerns companies with more than fifty (50) shareholders, regardless of the sector or industry in which they operate.
Please select either button for further information.
Be part of a groundbreaking event where industry leaders and experts will gather to explore the future of capital markets. Don’t miss your chance to connect, learn, and engage with key players in the industry. Reserve your spot now!