ቅሬታ

እራስዎን ከመጭበርበር እና ሽፍጥ ይጠብቁ። ማወቅ ያለብዎት ነገር ይኸውና

ማጭበርበርን ማወቅ

እያንዳንዱ ኢንቨስትመንት የአደጋ ስጋት ይኖረዋል።የኢካገባ ከሌሎች የህግ አስከባሪ አካላት ጋር በመተባበር መዋቅራዊ ስጋቶችን ለመቀነስ እና ኢንቨስተሮችን በመረጃ እጦት እና መረጃዎች ይፋ ባለመሆን ምክንያት ከሚፈጠሩ አደጋዎች ለመጠበቅ እየሰራ ነው። ነገር ግን ኢንቨስተሮች ራሳቸውን ከአጭበርባሪ ኩባንያዎች እና ኢንቨስትመንቶች መጠበቅ አለባቸው። የተለመዱ ማሳሳቻዎች የሚባሉትም የተረጋገጠ ትርፍ እንዳለዎት የሚያስመለሱ የተስፋ ቃሎች፣ በፍጥነት ምላሽ እንዲሰጡ የሚደረጉ የሚገፋፉ እና የተጋነኑ ማስታወቂያዎችን ያካትታሉ።

ሁሌም ቢሆን

  • የኢንቨስትመንት ውሳኔዎችን ከማድረግዎ በፊት የኢካገባ ፈቃድ ያላቸው የኢንቨስትመንት አማካሪዎችን ያማክሩ

  • የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴዎን ፈቃድ ባለው የካፒታል ገበያ አገልግሎት አቅራቢዎች እንደ ደላላ፣ ገበያ አገናኞች፣ የኢንቨስትመንት ባንኮች እና ጠባቂዎች በኩል ያድርጉ።

  • በኢካገባ የተመዘገቡ ሰነደ ሙዓለ ንዋዮችን ይገበያዩ።
  • ኢንቨስት ከማድረግዎ በፊት እንደ ደንበኛ ሳቢ መግለጫ ያሉ የአውጭዎች የመረጃ ሰነዶችን በደንብ ያንብቡ።

ሪፖርት

እነዚህን እና መሰል ተግባራትን ካዩ ሪፖርት ያድርጉ።

  • የገበያ ሽፍጥ፣

  • የውስጥ አዋቂ ግብይት፣
  • ሃሰተኛ/አሳሳች መረጃ

  • የሃሰት ግብይት
  • የተጭበረበረ ግብይት

የካፒታል ገበያ አስተዳደራዊ ፍርድ ቤት

የካፒታል ገበያ አስተዳደራዊ ፍርድ ቤት በአዋጅ ቁጥር 1248/2013 በባለስልጣኑ ወይም ለባለስልጣኑ በተሰጠው ስልጣን ወይም ተግባር የሚሰራ ሰው የሚሰጣቸው ውሳኔዎች ላይ የሚኖሩ ቅሬታዎችን ለማድመጥ እና ለመፍታት የተቋቋመ ነው።

ስልጣኑ የተዋቀረ እና ገለልተኛ የግምገማ ሂደትን እንዲኖረው ያስችላል፣ ይህም ባለድርሻ አካላት ፍላጎታቸውን የሚነኩ ውሳኔዎችን በድጋሚ እንዲታዩ ያስችላቸዋል። አስተዳደራዊ ፍርድ ቤቱ ራሱን ችሎ የሚንቀሳቀስ ሲሆን የአስተዳደር ተግባራቶቹን ለማስተዳደር በሰብሳቢው ፣ በመዝገብ ቤት እና ሌሎች አስፈላጊ ሰራተኞች ይደገፋል። ውሳኔዎችን በብቃት እንዲፈጽም በፍትሐ ብሔር ሥነ ሥርዓት ሕጎች መሠረት ለመደበኛ ፍርድ ቤቶች በተሰጠው ሥልጣን ይሰራል።

መዋቅር እና አባልነት

ፍርድ ቤቱ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተሾሙ አምስት አባላት ያሉት ሲሆን ሰብሳቢ፣ ምክትል ሰብሳቢ እና ሌሎች ሶስት አባላትን ያካተተ ነው። ሰብሳቢው እና ምክትል ሰብሳቢው በሰነደ ሙዓለ ንዋዮች፣ በንግድ ስራ፣ ፋይናንስ ወይም ሂሳብ አይያዝ ልምድ እና የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኛ ሆኖ ለማገልገል የሚያስችል ብቃት ሊኖራቸው ይገባል።

የተቀሩት ሶስት አባላት በህግ፣ በሰነደ ሙዓለ ንዋዮች፣ በንግድ ስራ፣ በፋይናንስ ወይም ሂሳብ አያያዝ እውቀት እና ልምድ ሊኖራቸው ይገባል።

ይግባኝ እና የውሳኔ ሂደት

ፍርድ ቤቱ የይግባኝ ማመልከቻ በቀረበ በ60 ቀናት ውስጥ ውሳኔ ይሰጣል። የሚሰጠው ውሳኔ ዝርዝር እና ማስረጃ ግኝቶችን መሰረት ያደረገ ሲሆን  በባለስልጣኑ የተደረገውን ውሳኔ ወይም ድርጊት ሊያጸናው፣ ሊለውጠው፣ ሊሽረው  ወይም ባለስልጣኑ ጉዳዩን በድጋሚ እንዲመለከተው  ከመመሪያ ጋር መልሰው ሊልኩ ይችላሉ።

በውሳኔው ቅር የተሰኘ አካል ውሳኔውን ባወቀ በ 30 ቀናት ውስጥ በህግ ጉዳይ ብቻ ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይግባኝ ማቅረብ ይችላል።

 

ኢሜል complaints@ecma.gov.et

ቅሬታ ያቅርቡ

    Generic selectors
    Exact matches only
    Search in title
    Search in content
    Post Type Selectors

    Public Announcement

    This public notice is directed at publicly held companies established or raising capital through public subscription under the Commercial Code of Ethiopia. Specifically, it concerns companies with more than fifty (50) shareholders, regardless of the sector or industry in which they operate.
    Please select either button for further information.

    Capital Market Summit 2024

    Be part of a groundbreaking event where industry leaders and experts will gather to explore the future of capital markets. Don’t miss your chance to connect, learn, and engage with key players in the industry. Reserve your spot now!