ስለ እኛ

በጠንካራ የገበያ ቁጥጥር እና ልማት የኢትዮጵያን የወደፊት የፋይናንስ አቅም ማጎልበት።

ስለ እኛ

የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያዎችን የመቆጣጠር እና የካፒታል ገበያዎቹን እድገት እና ልማት የማበረታታት ኃላፊነት ያለበት ተቆጣጣሪ አካል ነው። በእርስዎ እና በእኛ ኃይል እናምናለን፣ እጅ ለእጅ በመሥራት የእርስዎን የዓመታት ጠንካራ ሥራ ወደ ቀላል፣ ደህንነቱ የተጠበቀ እና ግልጽ ኢንቨስትመንት እናሳድጋለን።

ዓላማችን

አካታች ፋይናንስ ለጋራ ብልጽግና

ራዕያችን

በፈጠራ እና በቁጥጥር ልህቀት ፈር ቀዳጅ የካፒታል ገበያ ተቆጣጣሪ ለመሆን።

ተልዕኳችን

ፈጠራን እና የፋይናንስ አካታችነትን የሚያበረታታ እና ቀጣይነት ያለው የኢኮኖሚ እድገትን የሚያመጣ የደመቀ የካፒታል ገበያ ስነ-ምህዳር ለማዳበር።

እሴቶቻችን

ተጠያቂነት

ታማኝነት

ነፃነት

ልህቀት

የእኛ ሚና እና ኃላፊነቶች

ኢካገባ በኢትዮጵያ የካፒታል ገበያዎች ቁጥጥር እና ልማት ውስጥ ቁልፍ ሚና ይጫወታል። የእኛ ኃላፊነቶች የሚከተሉትን ያካትታሉ:-

  • የአክሲዮን ልውውጦችን/ የአክሲዮን ገበያዎችን፣ ደላሎችን እና ሌሎች አማላጆችን/ አገናኞችን ጨምሮ የገበያ ተሳታፊዎችን ፈቃድ መስጠት እና መቆጣጠር።
  • የገበያውን ታማኝነት፣ ግልጽነት እና ቅልጥፍናን የሚያረጋግጡ ደንቦችን ማዘጋጀት እና ማስፈጸም።
  • ፍትሃዊ አሰራርን በማስተዋወቅ እና የገበያ ስጋቶችን በመቀነስ ባለሀብቶችን መጠበቅ።
  • የተለያዩ የገበያ ተሳታፊዎችን ፍላጎት ለማሟላት የተለያዩ የፋይናንስ ምርቶችን እና አገልግሎቶችን ልማት ማመቻቸት።
  • የካፒታል ገበያ ግንዛቤን እና መረዳትን ለማሳደግ የመንግስት አካላትን፣ የፋይናንስ ተቋማትን እና ህዝቡን ጨምሮ ከባለድርሻ አካላት ጋር መሳተፍ/ ግንኙነት መፍጠር።

ጉዟችን

የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን በሰኔ 2013 ዓ.ም ራሱን የቻለ የፌዴራል መንግሥት ኤጀንሲ ሆኖ በይፋ ተቋቁሟል። አፈጣጠሩ/ አጀማመሩ የፋይናንሺያል ሴክተሩን / የፋይናንስ ዘርፉን ነፃ ለማድረግ እና የግል ኢንቨስትመንትን ለማበረታታት ያለመው የኢትዮጵያ ሰፊ የኢኮኖሚ ማሻሻያ አካል ነበር። ኢ.ካ.ገ.ባ (ECMA) የተቋቋመው በአዋጅ ቁጥር 1248/2021 ሲሆን ይህም የአገሪቱን ታዳጊ የካፒታል ገበያ የመቆጣጠር ስልጣኑን ሕጋዊ መሠረት ይሰጠዋል። የኢ.ካ.ገ.ባ (ECMA) የመጀመሪያው ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ብሩክ ታዬ ባለሥልጣኑን ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ የመሩት ሲሆኑ ቆይታቸው መሠረታዊ የቁጥጥር ማዕቀፎችን በማዘጋጀት እና የካፒታል ገበያ ተቋማዊ አቅምን በማሳደግ ላይ ያተኮሩ ናቸው/ ነበሩ። በነሐሴ 2016 ዓ.ም ወ/ሪት ሃና ተኸልኩ/ቁ ሲተኳቸው በሕግ፣ በጠቅላላ ወንጀል ምርመራ እና በፋይናንሺያል ወንጀል ምርመራ ዕውቀትን በማምጣት አዲስ የተጠናከረ የቁጥጥር አፈፃፀም እና የገበያ ተዓማኒነትን አመላክተዋል።

ኢ.ካ.ገ.ባ (ECMA) ግልፅ እና ቀልጣፋ የካፒታል ገበያን በኢትዮጵያ ለመገንባት ቁርጠኛ ነው።

ሃና ተኸልኩ

ዋና ዳይሬክተር፣ ኢ.ካ.ገ.ባ (ECMA)

ወደ ፊት ስንመለከት

የኢትዮጵያን የካፒታል ገበያ ማዳበር እና ማጠናከር ስንቀጥል፣ ኢ.ካ.ገ.ባ (ECMA) ጠንካራ፣ ተቋቋሚ እና አካታች የፋይናንሺያል/ የፋይናንስ ሥርዓት የመገንባት ተልዕኮውን በቁርጠኝነት ይቀጥላል። የኢትዮጵያን የረዥም ጊዜ የኢኮኖሚ ግቦችን የሚደግፍ የበለፀገ የካፒታል ገበያ ራዕያችንን ለማሳካት ከአጋሮቻችን እና ከባለድርሻ አካላት ጋር አብሮ ለመስራት በጉጉት እንጠብቃለን።

የዳይሬክተሮች ቦርድ

ወ/ት ሃና ተኸልኩ

የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር

ማሞ ምሕረቱ እስመለዓለም

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ

ገብረኢየሱስ ጎንትዬ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የቦርድ አማካሪ

አባት አበበ ዋጋው

ጠበቃ እና የፋይናንስ አማካሪ (የቀድሞ AAU የአካዳሚክ ሰራተኞች)

ወንድምአገኘሁ ነገራ

ዋና ስራ አስፈፃሚ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ (ECX)

ዶ/ር ኢዮብ ተስፋዬ

የፕሮግራም ዳይሬክተር፣ UNCDF

አጫጭር መረጃዎች

የኢትዮጵያን የካፒታል ገበያ ለመቆጣጠር እና ለማልማት የተቋቋመ።

ተልዕኮ

በፋይናንሺያል ሴክተር ውስጥ ግልፅነትን፣ ታማኝነትን እና እድገትን ማሳደግ።

የገበያ ቁጥጥር

በገበያ ተሳታፊዎች መካከል ፍትሐዊ አሠራርን እና ተገዢነትን ያረጋግጣል።

የኢንቬስተሮች ጥበቃ

የሀገር ውስጥ እና የውጭ ኢንቬስተሮችን ጥቅም ይጠብቃል።

የፈጠራ ድጋፍ

የገበያ ቅልጥፍናን ለማሳደግ የፋይናንስ ፈጠራን ያበረታታል።

የትምህርት መርሃ ግብር

ለኢንቨስተሮች እና ባለድርሻ አካላት ግብዓቶችን እና ትምህርትን ይሰጣል።

ዓለም አቀፍ የጥራት ደረጃዎች

የኢንቬስተር እምነትን ለማጎልበት ከዓለም አቀፍ መልካም ተሞክሮዎች ጋር ይጣጣማል።/ ከዓለም አቀፍ ተሞክሮዎች ጋር በመጣጣም የኢንቨስተር እምነትን ያጎለብታል።